በአፍሪካ ለሚመጣው የ COVID-19 ክትባት ለመክፈል ፈቃደኛነትን የምርምር ጥናት ለማካሄድ አየተባበረ ይገኛል ፡፡ ይህንንም ዓላማ ለማሳካት፣ የዳሰሳ ጥናት ምላሽ በመስጠት የእርሶን ትብብር እንጠይቃለን ፡፡
ወደዚህ የዳሰሳ ጥናት እንኳን በደህና መጡ
የዳሰሳ ጥናቱ ዓላማ: "Future rural Africa" የትብብር ምርምር ማዕከል ከአጋሮቹ ፣ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ (ኢትዮጵያ) ፣ ካባሌ ዩኒቨርሲቲ እና አፓታ ኢንሳይትስ (ኡጋንዳ) ፣ የቦን ዩኒቨርሲቲ (ጀርመን) ፣ ኒው ሳውዝ ዌልስ ዩኒቨርሲቲ (አውስትራሊያ) እና ላይደን ዩኒቨርሲቲ (ኔዘርላንድስ) ጋር በአፍሪካ ለሚመጣው የ COVID-19 ክትባት ለመክፈል ፈቃደኛነትን የምርምር ጥናት ለማካሄድ አየተባበረ ይገኛል ፡፡ ይህንንም ዓላማ ለማሳካት፣ የዳሰሳ ጥናት ምላሽ በመስጠት የእርሶን ትብብር እንጠይቃለን ፡፡ በ ዳሰሳ ጥናት ለመሳተፍ 18 ዓመት እና ከዚያ በላይ መሆን አለብዎት ፡፡
ከዳሰሳ ጥናቱ ምን ይጠብኩቁ: ጥናቱ ለማጠናቀቅ ከ 15 ደቂቃ በታች ሊወስድ ይገባል። የተለያዩ መረጃ (ዕድሜ ፣ ጾታ ፣ የትምህርት ደረጃ እና ሙያ) እንዲመዘግቡ ይጠየቃሉ። ጥናቱ ከዚያ COVID-19 በኑሮዎ (በገቢዎ) ላይ ምን ያህል ተጽዕኖ እንዳሳደረ ፣ በሀገርዎ ባለው የጤና ስርዓት ላይ ያለዎትን የመተማመን ደረጃ እና አሁን እንዴት ጤንነትዎን እንደሚገመግሙ ይጠየቃሉ ፡፡ በስተ መጨረሻ፣ የዳሰሳ ጥናቱ የ COVID-19 ክትባት በአከባቢው ገበያ የሚቀርብ ከሆነ ለመክፈል ያለዎትን ፍላጎት ይገመግማል ፡፡
ጥናቱ በአራት ቋንቋዎች ማለትም በእንግሊዝኛ ፣ በስዋሂሊ ፣ በአማርኛ እና በኪንያሪያዋን ይሰጣል ፡፡ በሚመቻቸው ቋንቋ ምላሽ መስጠት ይችላሉ፡፡ እባክዎን ጥያቄዎቹን በጥንቃቄ ያንብቡ እና በቅንነት ይመልሱ ፡፡
ማስተባበያ: ከተመራማሪዎቹ ወይም ከተቋሞቻቸው መካከል አንዳቸውም በማንኛውም የ COVID-19 ክትባት ልማት ተግባራት ውስጥ አይሳተፉም ፡፡ ከ COVID-19 ክትባት ጋር ከተያያዘ ማንኛውም ኩባንያ ገንዘብ አላገኙም ፡፡ ይህ ጥናት ሙሉ በሙሉ የምርምር ፍላጎት ያለው ሲሆን ቀጣይነት ባለው የ COVID-19 ክትባት ተነሳሽነት ላይ ምንም ዓይነት ተጽዕኖ ዓይኖሮውም፡፡ ከምርምር ውጭ የሚገለፁት አስተያየቶች የተመራማሪዎቹ ብቻ እንጂ ተቋሞቻቸውን የማይወክሉ ይሆናሉ ፡፡
- ስለ COVID-19 ክትባቶች ተነሳሽነት መረጃ እባክዎን የዓለም የጤና ድርጅቶችን ገጽ ይጎብኙ እዚህ
- የ COVID-19 መከላከያ መረጃን ለማግኘት እባክዎ የዓለም ጤና ድርጅት ድር ጣቢያዎችን እዚህ ወይም the Centers for Diseases Control እዚህ ይጎብኙ::